የመንግስታቱ ድርጅት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የተመድ የሰብአዊ መብቶች የባለሙያዎች አጣሪ ኮሚሽን የስልጣን ዘመን ለአንድ ዓመት አራዘመ።
ምክር ቤቱ የኮሚሽኑን የስልጣን ዘመን ያራዘመው በትግራይ ከባድ የሰብአዊ መበት ጥሰቶች መፈፀማቸው አሳማኝ ምክንያቶች በመኖራቸው መሆኑን በውሳኔው ተማላክቷል።
ውሳኔው የፀደቀው በሃያ አንድ የምክር-ቤቱ አባል ሃገራት ድጋፍ በአስራ ዘጠኝ ተቃውሞ በሰባት ድምፅ ተአቅቦ ነው።
በርካታ የአፍሪካ ሃገራት የኮሚሽኑ የስልጣን ዘመን እንዳይራዘም በመቃወም ዳግም አሳፋሪ ታሪክ በመፈፀማቸው የዓለም ዓቀፍ ሚድያ መነጋገሪያ ሆኗል።