Home ዜና በአፍሪካ ህብረት ሊካሄድ ታስቦ የነበረው  የሰላም ድርድር ተራዘመ

በአፍሪካ ህብረት ሊካሄድ ታስቦ የነበረው  የሰላም ድርድር ተራዘመ

1156

በአፍሪካ ህብረት አዘጋጅነት በትግራይ መንግስትና በፋሽስቱ የአብይ ቡድን መካከል በመጪው እሁድ መስከረም 29 ቀን 2015 ዓ.ም ሊካሄድ ታስቦ የነበረው የሰላም ድርድር መራዘሙን ሮይተርስ የዜና ወኪል ዘገበ።

ሮይተርስ የዜና ወኪል የዲፕሎማቲክ ምንጮችን ዋቢ አድርጎ እንደዘገበው የታቀደው የሰላም ንግግር እንዲዘገይ የተደረገው በሎጀስቲክ ምክንያት ነው።

በተመሳሳይ የቀድሞ የኬንያው ፕሬዝዳንት እሁሩ ኬንያታ በሰላም ውይይቱ ለመገኘት እንደማይችሉ ዛሬ ያስታወቁ ሲሆን በቀጣይ ስለውይይቱ ሂደት ግልፅ የሆነ ማብራርያ እንደሚሹም ገልፀዋል።