Home ዜና የትግራይ ተወላጅ አትሌቶች ድልና ደስታ ከቤተሰብ ጋር መጋራት አለመቻል

የትግራይ ተወላጅ አትሌቶች ድልና ደስታ ከቤተሰብ ጋር መጋራት አለመቻል

961

የአትሌት ለተሰንበት ግደይ ወላጆች ፋሽስቱ የአብይ ቡድን ባኖረው ከበባና ክልከላ ልጃቸው በአለም መድረክ ያስመዘገበችውን ድል መስማትም ሆነ ማየት እንዳልቻሉ ገለፁ።

የትግራይ ተወላጆች ለዚች አገር እልፍ መስዋእትነት ከፍለው ባቀንዋት እልፍ ሳይጠይቁ በማንነታቸው ብቻ የባእድ ጠላትን ጭምር ጋብዘው በትግራይ ተወላጆች ላይ ያልተነገረ እንጂ ያልተደረገ ግፍ የለም፡፡ ክህደት እና ጭፍጨፋ መልስዋ ላደረገችው ለዚች ሃገር ግን አሁንም እልፍ መስዋእትነት እየከፈሉ ይገኛሉ፤ ልጅ መውለድ የለበትም ተብሎ ባእድ ነገር ለገባበት ለፈረዱላት የትግራይ እናት ማህፀን የፈሩት ጀግኖች አትሌቶች እየተገፉም ቢሆን ኢትዮጵያን አስጠርተዋል፡፡

የትግራይ ተወላጆች ለዚች አገር እልፍ መስዋእትነት ከፍለው ባቀንዋት እልፍ ሳይጠይቁ በማንነታቸው ብቻ የባእድ ጠላትን ጭምር ጋብዘው በትግራይ ተወላጆች ላይ ያልተነገረ እንጂ ያልተደረገ ግፍ የለም፡፡ ክህደት እና ጭፍጨፋ መልስዋ ላደረገችው ለዚች ሃገር ግን አሁንም እልፍ መስዋእትነት እየከፈሉ ይገኛሉ፤ ልጅ መውለድ የለበትም ተብሎ ባእድ ነገር ለገባበት ለፈረዱላት የትግራይ እናት ማህፀን የፈሩት ጀግኖች አትሌቶች እየተገፉም ቢሆን ኢትዮጵያን አስጠርተዋል፡፡

በአሜሪካ ኦሪጎን እየተካሄደ ባለው 18ኛው የአለም አትሌክስ ሻምፕዮና በ10.000 ሜትር ርቀት የወርቅ መዳልያ አሸናፊ የአትሌት ለተሰንበት ግደይ ወላጆች ከተገናኙ ሁለት አመት እነዳለፋቸውና አሁንም ቢሆን ይህንኑ አኩሪ ድል ለማየትም ሆነ ለመስማት አልታደሉም፡፡ 

በአምባገነኑ ኢሳያስ ሰራዊት ከፍተኛ የንብረት ዘረፋ የደረሰባቸው የአትሌቷ ቤተሰቦች በከበባው ምክንያት ከልጃቸው ድጋፍ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ታውቋል።