Home ዜና ፋሽስቱ የአብይ ቡድን አሁንም ሰብአዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ያለ ምንም ቅድመ ኔታ...

ፋሽስቱ የአብይ ቡድን አሁንም ሰብአዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ያለ ምንም ቅድመ ኔታ እንዳይገባ እንቅፋት መሆኑ ተገለፀ፡፡

1829

ፋሽስቱ የአብይ ቡድን ለሰላም ዝግጁ ነኝ ቢልም አሁንም ሰብአዊ እርዳታ ወደ ትግራይ ያለ ምንም ቅድመ ኔታ ሁእንዳይገባ እንቅፋት ሆኖ እየቀጠለ መሆኑን የትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ገለፁ።

ፋሽስቱ የአብይ ቡድን ለሰላም ዝግጁ ቢሆን ኑሮ የህዝብ አገልግልቶችን ክፍት ማድረግ ነበረበት ያሉት ዶ/ር ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል በUSAID አማካኝነት ነዳጅ ይዘው ወደ ትግራይ ለመግባት የተዘጋጁ ጥቂት ተሽከርካሪዎች ቢኖሩም ፋሽስቱ የአብይ ቡድን ፈቃድ ባለመስጠትና በማስተጓጎል እንቅፋት እየፈጠረ ነው ብለዋል።

በዚህ ምክንያትም ወደ መቐለ የገባው እህል ወደ ተረጂዎች እንዳይዳረስና የትግራይ ህዝብ በህመምና ረሃብ እንዲሰቃይ ፋሽስቱ ቡድን መስራቱን አጠናክሮ ቀጥሎበታል ሲሉም ገልፀዋል።