Home ዜና የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ዛሬ መቐለ ገቡ፡፡

የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ ዛሬ መቐለ ገቡ፡፡

735

የአፍሪካ ሕብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልእክተኛ የሆኑት ኦሊሴጎን ኦባሳንጆ በቀጠናዊ ጉዳዮች ከትግራይ መንግስት ባለስልጣኖች ለመነጋገር ዛሬ መቐለ ከተማ ገቡ፡፡

የትግራይ መንግስት ቃል አቀባይ አቶ ጌታቸው ረዳ እንደገለፁት ልዩ መልእክተኛው ከትግራይ መንግስት ፕሬዝዳንት ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል(ዶ/ር) ጋር ተገናኝተው በቀጠናዊ ጉዳዮች ላይ ተነጋገረዋል፡፡

ኦባሳንጆ በትግራይ ላይ የተከፈተው የጀኖሳይድ ጦርነት ለማስቆም እና ሰላማዊ መፍትሔ ለማምጣት በተደጋጋሚ ወደ መቐለና አዲስ አበባ እየተመላለሱ የሰላም ጥረት እያደረጉ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡